Sagalicha Dhiigicha Hafuurichaቃሉ ደሙ መንፈሱ |
|||||||
The Word the Blood the Spirit |
|||||||
|
የጥናት 4
የጥናቱ መግብያ የጥናቱ ዓላማ፡(ለአስጠኚ ብቻ) ተሳታፊዎች የጸሎት ሕይወታቸውንና ይዘታቸውን በእግዚአብሄር ቃል እንዲመረምሩ ለመርዳት፡፡ የጥናቱ ጥያቄዎች 1. የጥናት ክፍሉን ቢያንስ ሁለት ጊዜ በጋራ አንብቡ፡፡ 2. የጥናት ክፍሉን ሓሳብ በራስህ ቋንቋ ለቡድንህ ተናገር፡፡ 3. ‹‹›ጸጥና ዝግ ብለን አንድንኖር› የሚለውን ሓረግ እንዴት ትረደዋለህ? የጸጥታና ዝግታ አለመኖር እንዴት አድርገው ‹‹(እግዚአብሄርን በመምሰልና በጭምተኝነት›› መኖርን ይከለክላሉ? (ኤር29፡7) 4. ‹‹ልመና፣ጸሎት፣ ምልጃና ምስጋና›› ምን ልየነትና ሕብረት አላቸው? የአንቴ ሕይወት የትኛው ምዛንን ይደፋል? ለምን? 5. ቤቴክርስቲያን ‹‹ስለ ሰዎች ሁሉ›› እንዴት ያገባታል? የእኛስ ቤቴክርስቲያን ስለ ሰዎች ሁሉ ትጸልያለችን? (ቁ.3-4፣2ጴጥ.3፡3-9፤ ከቤቴ/ያን ዕልሁና ዓላማ ጋር በማያያዝ ማየትም ይጠቅማል፡) 6. እግዚአብሄር ሰዎች ሁሉ እንዲያውቁት የሚፈልገው ‹‹እውነት›› የትኛው ነው? (ኢሳ.53፡10-11፤ ዮሃ.14፡6፣ 7. ከመዳንና እውነትን ከማወቅ የትኛው ይቀድማል? ስለዚህ የተቀመጠበት አሰላለፍ በቅደም ተከተል ላይ ወይስ በአብሮነታቸው ላይ የሚያተኩር ይመስልሃል? 8. በቁ.4 ላይ የተገለጠው ‹‹መዳን/ እንዲድኑ የሚለው ቃል›› ምን ማለት ነው? ከምን ይዳናል? አንድ ሰው ይህንን አይነቱን መዳን እንዴት ማግኘት ይችላል?(ተጨማሪ ቁ.3፣ኢሳ.45፡22፣ ሕዝ.18፡21-23፣33፡10-11፣ ዮሃ.3፡14-18፤ 2ቆሮ.5፡17-21፣የሓ.ሥ4፡8-12፤ሮም3፡10-26 አንብቡ) 9. በጥያቄ 8 ውስጥ ባደረጋችሁት ምርመራ፣ ስለራስህ መዳን እርግጠኛ መሆን ትችላለህን? ስለመዳንህ እርግጠኛ የሚያደርግህ ምን ነገር አገኘህ? (በተጨማሪም ዮሃ.10፡25-30፣ 1ዮሃ.5፡10-15፤1ጰጥ.1፡10-11 አንብቡ፡፡) 10. ከዚህ ጥናት ተነስተህ በጸሎት ሕይወትህና በጸሎትህ ይዘት ላይ ምን ለውጥ አንዲመጣ ትፈልጋለህ?
ተክሉ ተ. ጉታ ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት
E-mail: [email protected]
|
Waaqayyo si jaallata
Ati Eessa? |
|||||