Sagalicha Dhiigicha Hafuuricha

ቃሉ ደሙ መንፈሱ

Header Image  

The Word the Blood the Spirit

    

 
 
 

 

ጥናት 15: 1ጢሞ.6፡1-5


መግቢያ
በህይወት ዘመናችን ውስጥ ሊገዳደሩን ከሚመጡ ነገሮች ዋነኞቹ፣ ስለእግዚብሄር ያለንን መልካም ነገር ለመበረዝና ከእምነታችን እኛን ለመጣል የሚመጡቱ አሉበት፡፡ በተለይ ደግሞ፣ እኛው ራሳችን በቁሳዊው ወይም በምድራዊው ነገር እየተጎዳን ባለንበት ወቅት፣ በመንፈሳዊውም ጉዳት እዳይደርስብን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልገናል፡፡

አንዱ ሌላው ወንድሙን እየጨቆነና እየበዘበዘ ባለበት ወቅት፣ የራስን ነጻነት እየፈለጉ፣ የእግዚአብሄርንም ክብር ማስጠበቅ በቀላሉ የሚደረግ ነገር አይደለም፡፡ በዚህ ዓይነቱ ተግዳሮት ውስጥ ምዛኑን የጠበቀና በእግዚአብሄር ዘንድ ያለው ሕብረት እንዳይጎዳ፣ አንድ የእግዚአብሄር ሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጤናማ ትምህርት መመሪያው ማድረግና እግዚአብሄርን መምሰል የሚባለውን ልብስ መጎናጸፍ ያስፈልገዋል፡፡
ከዛሬው ክፍል የምናጠናው ዋና ነገር ከዚህ ሓሳብ ጋር የተያያዜ ይሆናል፡፡

የጥናቱ ዓላማ
ተሳታፊዎች በእለት ተእለት ኑሮአቸው የሚያጋጥማቸው ማንናውም ካባድና ቀላል ተግዳሮት ለማሸነፍ በሚነሱበት ጊዜ፣ የጌታችንን ትምህርትና ሕይወት መሪህአቸው ማድረግ እንድለማመዱ ማበረታታት፡፡

የጥናቱ ክፍል 1ጢሞ.6፡1-5
ማጥኛ ጥያቄዎች
1. የጥናት ክፍሉን ደጋግማችሁ አንቢቡት፡፡

2. የምንባቡን አጠቃላይ ኣላማ በአንድ አጭር ዐረፍተ ነገር ተናገር፡፡

3. በዚህ ክፍል መሠረት፣ የእግዚአብሄር ስምና ክብር በአማን ወንድሞችና እህቶች የሚሰደበው መቼ ነው (2ሳሙ.12፡13-14፣ኢሳ.52፡4-7፣ ሕዝ.36፡16-23፣ሮሜ 2፡17-27፣1ቆሮ.10፡31-33፣1ጴጥ.3፡15-18)

4. በቁ1 ላይ ‹ክብር ሁሉ እንደተገባቸው ይቁጠሩ› የሚለውን ሃሳብ እንዴት ተረዳላችሁ? የባሪነት ስነስርዓትን ያስቀጥሉ ማለት ነውን? (ዘፍ. 16፡4-9፣ሚል 1፡5-9፤1ቆሮ 7:21-24; ኤፌ.6፡ 6-9፣ገላ.5፡1፤

5. በቁ2 መሠረት፣ አማኞች ክርስቲያን አስተዳዳሪዎችን ከሌሎች ይልቅ ማክበርና መታዘዝ ያለባቸውም ለምንድን ነው

6. በዚህ የጥናት ክፍል መሠረት፣ አንድ ሰው የሚያስተምረው ትምህርት ተቀባይነት የሚያገኘው በምን መለኪያ ተለክቶ ነው?(ሮሜ16፡17-18፣ገላ.1፡6-11፤1ጢሞ.1፡3-7)

7. በቁ.3-4 መሠረት፣ በእውቀት ማስተማሪን ‹በትዕብት ከመነፋት› ጋር የሚያመሳስለው ምን ዓይነት ሁኔታ ሲፈጠር ነው? (ቆላ.2፡16-19፣2ጴጥ.2፡4-16)

8. ራሳችሁን በጢሞቴዎስ ዘመን ጌቶቻቸውን ሲያገለግሉ ከነበሩት ባሮች ቦታ ቢታስቀምጡ፣ ይህ የጥናት ክፍል፣ እንዴት ሊጎዳችሁና ሊጠቅማችሁ ይችላል?

 

ተክሉ ተ. ጉታ

ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት

 

E-mail: [email protected]

 

 
 

Waaqayyo si jaallata
Waaqayyo si jaallata

Ati Eessa?
Ati Eessa?