Sagalicha Dhiigicha Hafuuricha

ቃሉ ደሙ መንፈሱ

Header Image  

The Word the Blood the Spirit

    

 
 
 

 

ጥናት 17: 1ጢሞ.6፡13-21


መግቢያ
በጥናት 14 አንድ ክርስቲያን በለው መርካት፣ እግዚአብሄርን መምሰልን ደግሞ ለገንዘብ/ቁሳዊ ትርፍ መጠቀም እንደለሌበት አይጠናል፡፡ በክፍሉ መሠረት ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ተደርጎ ተገልጦአል፡፡ በተጨማሪም ሰው እግዚአብሄርን መፍራት የሌለበት ሀብት ፍላጎት ሲኖረውና፣ ገንዘብን ብቻ ማግኘትን ዓላማው አድርጎ ከኖረ ብዙ ዓይነት ችግሮች እንደሚያጋጥሙት ከመጽሓፍ ቅዱሳችን አጥንተን ነበር፡፡

በመጨረሻም የእግዚአብሄር ሰው ከገንዘብ ፍቅር መሸሽና በአንጻሩ ደግሞ ‹ጽድቅን፣ እግዚአብሔርን መምሰልን፣ እምነትን፣ ፍቅርን፣ መጽናትንና የዋህነትን መተከታተል› (ቁ11) እንዳለበትና ከሁሉም አብልጦ በክርስቶስ ያገኘውን የዘላለምን ሕይወት መያዝ እንዳለበት አጥንተናል ፡፡

በዛረው ጥናት ደግሞ ለምንና እነዴት በእግዚአብሄር ፍት መመላለስ እንዳለብን፣ በሓብታች እንደት መመልከትና መጠቀም እንዳለብንና እውነተነውን እውቀት ለይተን መያዝ እንዳለበን እናጠናለን፡፡
የጥናቱ ዓላማ
ተሳታፊዎች የዘላለም ሕይወትን መያዝና ተስፋቸውንም በሚጠፋው ሓብት ለይ ሳይሆን ዘላለማዊ በሆነው በእግዚብሄር ላይ ማድረግ እንዲችሉናና በመልካም ነገርም ለመበልጸግ እንዲነሳሱ መርዳት፡፡

የጥናቱ ክፍል 1ጢሞ.6፡13-21
ማጥኛ ጥያቄዎች
1. የጥናት ክፍሉን ደጋግማችሁ አንቢቡት፡፡

2. የምንባቡን አጠቃላይ ኣላማ በአንድ አጭር ዐረፍተ ነገር ተናገር፡፡

3. ‹‹ያለ እድፍና ያለነቀፋ ሆነህ ትእዛዙን ጠብቅ›› በሚለው ምክር ውስጥ፣ እድፍና ነቀፋ ምንድናቸው?

4. በ13-16 በተገለጠው መሠረት፣ ስለጌታችን ዳግሞ መገለጥና ስለእርሱ ማንነት መረዳት የዛሬውን ሕይወታችን በአግባቡ ለመኖርና አገልግሎታችንንም በተገቢው ሁኔታ ለማድረግ እንዴት ሊረዳን ይችላል?

5. በመጽሓፍ ቅዱስ መሠረት፣ አንድ የእግዚአብሄር ሰው ሓብታም መሆን የለበትም የሚል የለም፡፡ ነገር ግን በንብረቱን ላይ ሊኖረው ስለሚገባው አመለካከትና በአጠቃቀሙ ላይ ብዙ መመሪያዎችና ምክሮች አሉ፡፡ በዚህ ጥናት ይህንን በተመለከተ የተሰጡትን ምክሮች አንድ በአንድ አውጡና ተወያዩበት፡፡(ቁ 17-19)፡፡

6. በቁ 20-21 ላይ የገጸው ‹‹እውቀት›› ምን ዓይነት እውቀት ነው፡፡ ዛሬ እኛን ልንሰማቸውና ሊንታለልባቸው በምንችል ተመሳሳይ ‹እውቀቶች› ላይ ተመካከሩ፡፡

7. ከዛሬው ጥናት ምን ተማራችሁ?

 

ተክሉ ተ. ጉታ

ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት

 

E-mail: [email protected]

 

 
 

Waaqayyo si jaallata
Waaqayyo si jaallata

Ati Eessa?
Ati Eessa?