Sagalicha Dhiigicha Hafuuricha

ቃሉ ደሙ መንፈሱ

Header Image  

The Word the Blood the Spirit

    

 
 
 

 

ጥናት 16: 1ጢሞ.6፡5-12


መግቢያ
አንድ ሰው በህይወት ዘመኑ ሁሉ የሚኖርለትና የሚጨነቅለት ልቡን ላስቀመጠበት ነገር ነው፡፡ ስኬቱ እንዴሆነ አድርጎ የሚቆጥረው ነገር፣ አረማመዱንና አስተሳሰቡን ሁሉ ይቃኜዋል፡፡ ከዚህ የተነሳ፣ አንዳንዶች ክርስትናን ለብልጽግና ፍለጋ እንዴመሳሪያ ይጠቀሙበታል(1ተሰ.2፡5)፡፡ ጳውሎስ ግን እንዲህ ያሉ ሰዎች ለቤቱ አገልግሎ መሾም እንደለለባቸው ደጋግሞ ጢሞቴዎስን ይመክር ነበር(3፡3፣8)፡፡

ጳውሎስ ደግሞ ጢሞቴዎስን ሲመክረው፣ ልቡን ሊያስቀምጥበት አስፈላጊ የሆነውን በመጠቆም፣ ሌሎችን ነገሮች ከመከተል እንድጠበቅ ይጠይቀዋል፡፡ ይህም የዘላለምን ሕይወት በመያዝ ነው ይለዋል፡፡ ጌታ ኢየሱስም በሚያስተምርበት ጊዜ፣ ሰው መዝገቡ ባለበት በዚያ ልቡ ደግሞ አለና፣ መዝገባችሁን በሰማይ ሰብስቡ ብሎአል፡፡

ጳውሎስም፣ ጢሞቴዎስ የዘላለምን ሕይወት ለመያዝ መከተል የሚገባቸውን የሕይወት ዘይቤያት ዘርዝሮ ይነግረዋል፡፡ በዚህ ጥናት እነዚያን ዝርዝሮችና በተቃራኒው ያሉትን ጥቅት ነገሮች እናጠናለን፡፡

የጥናቱ ዓላማ
ተሳታፊዎች በእለት ተእለት የክርስት ሕይወታቸውን በሚያስቡበት ጊዜ፣ የዘላለም ሕይወትን መያዝ ዋናው እንዴሆን አንድገነዘቡ መርዳት፡፡

የጥናቱ ክፍል 1ጢሞ.6፡5-12
ማጥኛ ጥያቄዎች
1. የጥናት ክፍሉን ደጋግማችሁ አንቢቡት፡፡

2. የምንባቡን አጠቃላይ ኣላማ በአንድ አጭር ዐረፍተ ነገር ተናገር፡፡

3. ከቁ 6-8 ባለው ክፍል ውስጥ እንዴተገለጸው ‹‹ኑሮዬ እበቃኛል›› ማለት ምን ማለት ነው? ሰው እንዲህ ማለት የሚችለው መቼ ነው? ዘኁል.24፡10-14፤2ጴጥ.2፡15-16፣ማቴ.6፡25-33፤13፡22፣ፍል4፡11-13፣ ዕብ.13፡5-6)

4. ‹‹እግዚአብሄርን መምሰል ማትረፍያ ነው›› የሚለውን አገላለጽ እንዴት ተረዳላችሁ?

5. በቁ.9-10 ላይ እንደተገለጸው፣ የሕይወት ዓላማቸውን ‹‹ባለጠጎች የመሆን ፍላጎት ብቻ›› ላይ የመሠረቱትን ሰዎች ምን ምን ችግሮች ያጋጥሟቸዋል? በእያንዳነዳቸውን አንድ በአንድ ተነጋገሩበት፡፡

6. ‹‹ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ስር ነው›› የሚለውን አገላለጽ እንደት ትረዱታለችሁ? (

7. እኛስ ገንዘብን መውደዳችንንና አለመውደዳችንን እንዴት ልናውቅ እንችላለን? ገንዘብ ወዳጆች ሆነን ራሳችንን ከአገኘንስ አሁንና ከአሁን በኋላ ምን ማድረግ ይኖርብናል? (ቁ 11-12 ንም አገናዝቡ)፡፡

 

ተክሉ ተ. ጉታ

ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት

 

E-mail: [email protected]

 

 
 

Waaqayyo si jaallata
Waaqayyo si jaallata

Ati Eessa?
Ati Eessa?