Sagalicha Dhiigicha Hafuurichaቃሉ ደሙ መንፈሱ |
|||||||
The Word the Blood the Spirit |
|||||||
|
ጥናት 11: 1ጢሞ.4፡7-12
በዚህ ጥናት ሁለተኛውን ነገር እንመረመራለን-- የእግዚአብሄርን ቃል በተግባር መለማመድ ፡፡ በተለይ በዚህ ጥናት ውስጥ ሓዋሪያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ሲጽፍ፣ እንዴት አድርጎ የሚገባውን (ከአገልግሎት ሕይወቱ ጋር የሚሄደውን) ለማድረግና የማይገባውን (ከእግዚአብሄር ፈቃድ ጋር የማይስማማውን) ደግሞ አለማድረግን መለማመድ እንዳለበት ይመክረዋል፡፡ ይህም ጢሞቴዎስንም ሁነ ከእርሱ የሚማሩት በክርስቶስ ላይ ያላቸውን እምነት የሚያስክድ እየበዛ በሚሄድበት ዘመን እምነታቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ ይረዳቸዋል፡፡ የጥናቱ ዓላማ ማጥኛ ጥያቄዎች 1. የጥናት ክፍሉን ደጋግማችሁ አንቢቡት፡፡ 2. ያነበባችሁትን ነገር በጭሩ በራስህ አገላለጽ ለቡድንህ ተናገር፡፡ 3. በዚህ ክፍል ውስጥ ጢሞቴዎስ እንዲያደርጋቸው የታዘዙለት የእምነት ጽናት መርጃዎች ምን ምን ናቸው (ቁ.7፣11-12፤ 4. በቁ.7u መሰረት፣ ‹‹ለአለም ከሚመችና የአሮግቶችን ሴቶች ጨወታ ከሚመስለው ተረት ራቅ›› የሚለውን ሃሳብ እንዴት ትረደዋለህ? (1ጢሞ.1:4; 6:20; 2ጢሞ.:2:16-25; 4:4) አሁን ባለንበት ጊዜና ሁኔታ ይንን ዓይነት እርምጃ አወሳሰድ እንዴት ተግባራዊ ልናደርግ እንችላለን? 5. በቁ.7ለ መሰረት፣ አንድ ሰው እግዚአብሄርን መምሰልን ራሱን ማስለመድ የሚችለው ምን ማድረግ ሲችል ነው? ይህ አይነቱ ነገር በእኛስ እንዴት መተግበር አለበት? (1ቆሮ.9፡ 24-27) 6. በቁ9 ላይ ‹‹ሁሉም መቀበል ይገባል›› የተባለው ሃሳብ ምንድን ነው? ሓሳቡን መቀበላችንስ በምን ይታወቃል? 7. በቁ 12 መሠረት፣ አንድ የእግዚአብሄር ሰው በሌሎች የሚናቀው መቼ ነው? እንዳይናቅስ በምን መከላከል ይችላል? (ለምሳሌ፡-የመርዶክዮስ ታርክ፤የዮሴፍ ታርክ፣) 8. ከላይ ያየናቸው ነገሮች በዘመናችን ካሉት የመጨረሻ ዘመን ስህተቶች አንዴት ሊጠብቁን እንደምችሉ ተወያዩበት፡፡
ተክሉ ተ. ጉታ ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት
E-mail: [email protected]
|
Waaqayyo si jaallata
Ati Eessa? |
|||||