Sagalicha Dhiigicha Hafuurichaቃሉ ደሙ መንፈሱ |
|||||||
The Word the Blood the Spirit |
|||||||
|
ጥናት 12: 1ጢሞ.4፡13-15
በዚህ ጥናት ሦስተኛውን ነገር እንመረመራለን-- በቃሉ ማደግ፡፡ በተለይ በዚህ ጥናት ውስጥ ሓዋሪያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ሲጽፍ፣ እንዴት አድርጎ በቃሉ ማደግ እንዳለበት ይመክረዋል፡፡ በተለይ ደግሞ በቃሉ ማደግን ከራሱና ከሌሎች ድነት ጋር አያይዞ ይነግረዋል፡፡ ምንም እንኳን ሰውን የሚያድነው ክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሄር ጸጋ ቢሆንም (ሮሜ.3፡19-25፣ ኤፈ.2፤1-8)፣ እምነት እንድኖርና እንድጠበቅ የእያንዳንዱ ሰው በቃሉ ማደግ፣ ይልቁንም ደግሞ የአገልጋዩ እድገት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ብዙዎችን ከእምነታቸው ወደ ሃላ የሚመልሳቸው ነገር በበዛበት ጊዜ፣ ሰዎች ሰምተው፣ ተምረውና አይተው የሚበረቱበት የቃሉ ንባብ፣ እንዴ ቃሉ የሆነ ምክርና ትምህርት ሰው ከእምነት ነገር እንዳይጠፋ ለማድረግ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ የጥናቱ ዓላማ የጥናቱ ክፍል 1ጢሞ.4፡13-15 2. ያነበባችሁትን ነገር በጭሩ በራስህ አገላለጽ ለቡድንህ ተናገር፡፡ 3. በቁ. 13 ላይ ያለው ማሳሰቢያ ከክርስቲያናዊ አገልግሎትና ሕይወት እድገት ጋር ምን ኣይነት ግንኙነት አለው? ለምን በማሳሰቢያ መልክ የተሰጠ የይመስልሃል? 4. በቁ 14 ላይ ያለው ‹ጸጋ›፣ በሮሜ 3፡ 19-25 ውስጥ ከተነገረው ‹ጸጋ› ጋር ምን ኣይነት ግንኙነትና ልዩነት አለው? 5. የእጅ መጫንን ትርጉምና አስፈላጊነት ተወያዩበት፣ አንድ ሰው በሌላው ላይ እጁን የምጭነው ዓላማ ነው? 6. በቁ15 መሠረት አንድ ክርስቲያን ሌሎች ሊመሰክሩት በሚችሉት መልኩ በብስለት ነገሮችን መናገርና ማድረግ የሚችለው ምን ሲያደርግ ነው? 7. በቃሉ ውስጥ የተገለጠልንን የእግዚአብሄር ፈቃድ ማሰብና ማዘውተር እንዴት አድርጎ ለአንድ ክርስቲያን ላይ የሚፈለገውን ሲከት (ማለትም ራሱ ድኖ ሌሎን ማዳንን) ሊያመጣ ይችላል? 8. ሰው በክርስቶስ አምኖ እንደምድን ብዙ የመጽሃፍ ቅድሱስ መረጃ አለ፡፡ እንዲህ ከሆን፣ በቁ 16 ላይ እንደተጻፈው ‹‹ለራስህና ለትምህርትህ መጠንቀቅ›› ከራስህና ከሌሎች ድነት ጋር እንዴት ይያያዛል? (መረጃ፣ ትምህርትህ የሚለው በቃል፣ በኑሮና በተግባር የሚናሳያቸውን አርአያነትንም የሚጨምር ሊሆን ይችላል)፡፡ 9. ከዛራ ጥናት የተማርከው አንድ ነገር ቢኖር ምንድን ነው?
ተክሉ ተ. ጉታ ቃሉ ደሙ መንፈሱ የወንጌል አገልግሎት
E-mail: [email protected]
|
Waaqayyo si jaallata
Ati Eessa? |
|||||